XtGem Forum catalog
free book gift

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።


Iqra

=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=

ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ


1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።

2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።

3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።

4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
Iqra
Iqra

Homeየወጣቱ ተልዕኮ ምንነትየአቂዳ ትምህርቶችየሶላት መመሪያረመዷንሙስሊም ሴቶችኢስላማዊ ቤተሰብከታሪክ ማህደርሐዲስለወጣቶችትምህርትና መሰረታዊ ክህሎታችጤናችንግጥምጥያቄና መልስኢስላማዊ መዝገበ ቃላት
free book gift

=<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=

ያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ!

free book gift

በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።

free book gift

ከችግር ጋር ምቾት አለ


የሰው ልጅ ሆይ ከረሃብ በኃላ ጥጋብ አለ ፣ ከጥማት በኃላም እርካታ አለ ፣ ከእንቅልፍ እጦት በኃላም እንቅልፍና ከበሽታ በኃላ ጤና አለ። የጠፋው ይገኛል ፤ የጠመመውም ይቃናል ፤ በአይን የተበላውም ይድናል ፤ ጨለማውም ይገፋል።

-<({አልቁርአን 76:9})>-

«አሏህም ድልን ወይም ከርሱ ዘንድ የኾነን ነገር እንዲያመጣ ይከጅላል።»

በተራሮች ላይ እና በየሸለቆዎቹ የሚያሳድደው ንጋት እንደሚመጣ ሌሊትን አብስረው ፣ የተጨነቀውንም ሰው በዓይን ጨረፍታ እና በብርሃን ፍጥነት የሚደርስ ድንገተኛ መፍትሄ እንደሚገኝ አብስረው ፤ አደጋ የደረሰበትንም ሰው ድብቅ መዳኛ እነደሚያገኝም አብስረው። በረሃው እየሰፋ መሆኑን ካየህ አረንጏዴ መስኮች እንደሚከተሉ እወቅ። ገመድም በኃይል ከተጎተተ እንደሚበጠስ እወቅ።

እምባን ተከትሎ ፈገግታ አለ ፤ ፍርሃትን ተከትሎ አማን ፣ ድንጋጤን ተከትሎ መረጋጋት አለ። ወደ አሏህ አንድነት የሚጣራውን ኢብራሂም እሳት ልታቃጥለው አልቻለችም ምክኒያቱም መለኮታዊው እንክብካቤ እሳትን «ቀዝቃዛና ሰላም ሁኚለት» የሚለውን የእዝነት መስኮት ከፍታለታለችና።

ባህሩም ሙሳን አላሰመጠችውም ምክኒያቱም እውነተኛውና ኃያሉ ድምፅ «ጌታዮ አብሮኝ አለ ይረዳኛልም» ብሏልና።

ነብዩ ሙሐመድ ሰ.ዐ.ወ ዋሻ ውስጥ ጏደኛቸውን ሲያፅናኑ «አሏህ ከኛጋር ነው» አሉ። በዚያም አማንን እርጋታንና በመጨረሻም ድልን አገኙ።

የአስቸጋሪ ጊዜያቸውና የነባራዊ ሁኔታቸው ባሮች ሁሌም የሚታያቸው ጥበት ፣ ችግር እና እድለቢስነታቸው ብቻ ነው። ምክኒያቱም ከቤቱ መግቢያ በር እና መስኮት ውጭ አሻግረው አይመለከቱም። ዓይኖቻቸውን ከግርዶው ጀርባ አሳልፈው ይመለከቱ ፤ አስተሳሰባቸውንም ከአጥሩ ጀርባ ያሻግሩ።

ራስህን አታጨናንቅ። ያለህበት መከራ እስከ መጨረሻው አይቀጥልምና ከዒባዳዎች(ከአምልኮዎች) በላጩ የአሏህን መፍትሄ መጠበቅ ነው። ቀናት ይገለባበጣሉ ፤ ዓመታትም ይለዋወጣሉ። የሩቅ ሚስጥሩም ድብቅ ነው። ጥበበኛውም ጌታ በየቀኑ በተለያዩ ጉዳዮች ውስጥ ነው ፤ ምናልባትም ከዚያ ብኃላ ሌላን ነገር ሊያስከትል ይችላል ፤ መከራንም ተከትሎ ምቾት ይመጣል።


379

የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
free book gift

Download Islamic Books
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ

Important Web Links


free book gift

free book gift

free book gift

ስለወጣቱ ተልዕኮ ምንነት ለማወቅ እዚህ ላይ ክሊክ ያድርጉ

Copyright©Youth-Mission የወጣቱ ተልዕኮ